Connect with us

All posts tagged "ሙፈሪያት ካሚል"

  • እሾሁን በጋራ... እሾሁን በጋራ...

    ነፃ ሃሳብ

    እሾሁን በጋራ…

    By April 5, 2021

    እሾሁን በጋራ… ሁሉም የሚያምረው በሀገር ነው። (ሙፈሪያት ካሚል) ሀገር ማለትም ሰዉ ነው፣ ሰዉነትም ነዉ። ሰውነት ደግሞ መከባበርን፣ መተሳሰብን፣ ርህራሄን፣ መደማመጥን፣ አንዱ የሌላዉን ህመም መታመምን ይሻል። ሁሉም የሚያምረው በሀገር ነው፣ ሀገር ሰላም መሆንን ትሻለች። ለዚህ ደግሞ መንግስት፣ መላው ህብረተሰብ በተደራጀ መንገድ እያንዳንዳችን እንደ ዜጋ በጋራ አንድ ሆነን ስንቆም ነው። ውድ ወገኖቼ! እጅግ የሚያሳዝኑ፣ ልብ የሚሰብሩ፣ የሚያሳፍሩም ጭምር ጭካኔ የተሞላባቸው ድርጊቶች በተለያዩ ጊዜያት አጋጥመዋል፣ እያጋጠሙም ይገኛል። ይቆጫሉ፣ ያበሳጫሉ፣ ያሳምማሉ፣ ያሳዝናሉ። መንስኤና መፍትሄዎቻቸውን ከመነጋገርና በጋራ ለመጋፈጥ ከመወሰን ውጪ አማራጭ የለንም። ከራሳቸው ጥቅም አኳያ የኢትዮጵያ መንገድ ያልተዋጠላቸው ሀይሎች ከዉስጥና ከዉጭ ካሉ ቡድኖች ጋር በመመሳጠር ሰላሟን የሚነሱ ልማቷን የሚያስተጓጉሉ፣ የዴሞክራሲ ትልሞቿን የሚገዳደሩ ስሱ(sensitive) አጀንዳዎችን ለይተዉ መስራት ከጀመሩ ዋል አደር ብሏል። ይህ ከውስጥ ድካማችን ጋር ተዳምሮ ጠላቶቻችን የሚመኙት ሁኔታ ውስጥ እንደምንገኝ ምን ያህል አስተዉለናል? ኢትዬጵያ ዉስጥ የብሄር ፣ የሀይማኖት ጉዳዮች እጅግ ስሱ (sensitive) መሆናቸው ይታወቃል። የጠላቶቻችን ስልትም እዚህ ላይ ያነጣጠረ ሆኖ የሞት የሽረት ትግል የሚያደርጉበት የዉስጥ ሁኔታችን ለዘመናት በዞሩ ዕዳዎችና በአዳዲስ ክስተቶች ድምር ውጤት መላጋት ምቹ ሁኔታ መሆኑን በመገምገም  ይህን በተለያዩ ስልቶች በማባባስ እንዳንደማመጥም ጭምር ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ መድቦ ሰፊ ርብርብ እያደረጉ ይገኛል። ብዙዎቹን እንቅስቃሴዎች እና ሙከራዎች በተግባር እያየናቸው ነው። እያስተዋልናቸው ነውን? መኖር፣ መታመም፣ መሞት፣ በወጉ መቀበር ማበድም ጭምር ሰላማዊ ሀገር ይሻሉ። ከያኒው እንዳለው “ሰው የሞተ እንደው በሀገር ይለቀሳል በሀገር …” ዉድ ወገኖቼ ሰክኖ መነጋገር የሚሹ በርካታ ዕዳዎች አሉን የጀመርነው አለ አጠናክረን መቀጠል የሚጠይቀን። አብዛኞቹ ዕዳዎች የትውልዱ ያልሆኑ ግን ተነጋግሮ የመፍታት ሀላፊነትን የተሸከምንበት ነው። ደግሞም ማድረግ የምንችለውና የሚገባን። ሀገር በትዉልዶች ቅብብሎሽ ነውና የምትገነባው። አዎ ባለዕዳዎች ነን። ለምን በዚህ ወቅት ሀገሬን በሁሉም አቅጣጫ ሰቅዞ መያዝ ተፈለገ?...

  • በመለያየትና በበላይነት ጎዳና የተገኘ ትርፍ የለም! በመለያየትና በበላይነት ጎዳና የተገኘ ትርፍ የለም!

    ነፃ ሃሳብ

    በመለያየትና በበላይነት ጎዳና የተገኘ ትርፍ የለም!

    By September 16, 2020

    በመለያየትና በበላይነት ጎዳና የተገኘ ትርፍ የለም! (ሙፈሪያት ካሚል) የበላይነትና የመለያየት ጎዳና ተጫጭኖት የቆየው አለም ይህ ጉዞ...

More Posts
To Top