Connect with us

ብሄራዊ ፓርኮችን ከእሳት አደጋ የሚከላከል ብርጌድ ተቋቋመ

ብሄራዊ ፓርኮችን ከእሳት አደጋ የሚከላከል ብርጌድ ተቋቋመ
ፎቶ :- ሰሜን ፓርክ

ዜና

ብሄራዊ ፓርኮችን ከእሳት አደጋ የሚከላከል ብርጌድ ተቋቋመ

ብሄራዊ ፓርኮችን ከእሳት አደጋ የሚከላከል ብርጌድ ተቋቋመ

በብሄራዊ ፓርኮች ላይ የሚከሰት የእሳት አደጋን የሚቆጣጠር የእሳት አጥፊ ብርጌድ ማቋቋሙን የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

በብሄራዊ ፓርኮች ላይ የሚከሰትን የእሳት አደጋዎች በአፋጣኝ ለመቆጣጠር ፓርኮቹን ከሚያጎራብቱ የህብረተሰብ ክፍሎች የመለመላቸውን የእሳት አጥፊ ብርጌዶች አሰልጥኖ ወደ ስራ ማስገባቱን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ ተናግረዋል፡፡

የእሳት አጥፊ ብርጌዶቹ በፓርኮች ላይ የእሳት አደጋ እንዳይከሰት ክትትል ከማደረጋቸውም በተጨማሪ ህብረተሰቡ በንቃት አካባቢውን እንዲቆጣጠር የማንቃት ስራ እንደሚሰሩም አክለዋል፡፡

በሌላ በኩል በፓርኮቹ ላይ የሚታዩትን ህገ-ወጥ የአደን ስራዎችን ለመቆጣጠር ግንዛቤ እየተሰጠ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡

ህገወጥ አደንና የእንስሳት ዝውውርን ለመቅረፍ ከሚሰጠው ግንዛቤ ባለፈ በተግባሩ የተሰማሩ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን አቶ ኩመራ አስረድተዋል፡፡

ባለስልጣኑ በዱር እንስሳት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ለመቀነስ ከሚሰራው ስራ ባለፈ የቱሪስት መዳረሻ መሰረተ ልማት አቅርቦትን ለማሻሻል መስራቱን ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ፎቶ :- ሰሜን ፓርክ

 

Click to comment

More in ዜና

Trending

Advertisement News.et Ad
To Top