Connect with us

“ኮሮናን እናሸንፈው!” – ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ

"ኮሮናን እናሸንፈው!" ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ
Photo: Facebook

ዜና

“ኮሮናን እናሸንፈው!” – ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ

“ኮሮናን እናሸንፈው!” ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ

ኮሮና ከሚያሸንፈን እናሸንፈው። ከሚዘምትብን እንዝመትበት። ከሚያጠፋን እናጥፋው።

የኮሮና ወዳጅ ማን እንደሆነ ደርሰንበታል። መዘናጋት ይባላል። ኮሮና ከመዘናጋት ጋር ከተባበረ አንችለውም። ሁለቱን መነጣጠል አለብን።

ሰሞኑን በኮሮና የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው። ለምን? ኮሮናና መዘናጋት ግንባር ፈጥረዋል ማለት ነው።

ኮሮና ማንን እንደሚጠላና እንደሚፈራ ዐውቀነዋል። ኮሮና ጥንቃቄ የሚባለውን ፈጽሞ አይወደውም።
ጥንቃቄ ባለበት ወይ አይደርስም ፤ ወይ የከፋ ጉዳት አያደርስም።

እንደምታዩት ሁለት፣ ሦስት፣ ዐሥር፣ ሠላሳ፣ ሰባ፣ እያለ መቶ ገብቷል።
ሁኔታው የሚያሳየው ኮሮና እያመረረ፣ እኛ እየተዘናጋን መምጣታችንን ነው።

ኮሮና ተዘናግቶ እኛ ብናመር ነበር ጥሩ።
ወይ ተባብረን እንነሣበት፤ አለያም ኮሮናና መዘናጋት ተባብረው ይደቁሱን?
ምርጫው ከሁለቱ አንዱ ነው?

ሁኔታው ሳይመርብን፣ እኛ እናምርበት። ኮሮና ሳያሸንፈን እናሸንፈው። ኮሮናን የማሸነፊያ ቀን ዛሬ፣ የማሸነፊያ ሰዓት አሁን፣ የሚያሸንፈውም ሰው እርስዎ ነዎት።

Click to comment

More in ዜና

Trending

Advertisement News.et Ad
To Top