Connect with us

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ልዋሃድ እችላለሁ አለ

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ልዋሃድ እችላለሁ አለ
Photo: Facebook

ዜና

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ልዋሃድ እችላለሁ አለ

ፓርቲው የምስረታ ጉባኤውን ባሳለፍነው ቅዳሜና እሁድ አካሂዶ ስሙን ከትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ወደ ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መቀየሩን አስታውቋል፡፡

ጉባኤውን በማስመልከትም ዛሬ በሰጠው መግለጫ በአላማ ከሚመስሉን የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር እስከ ውህደት በሚያደርስ ትብብር አብሮ ለመስራት ዝግጁ ነኝ ብሏል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም የትግራይ ህዝብ በአዲሱ የብልጽግና ፓርቲ ውስጥ ተወካይ የሌለው በመሆኑ ፓርቲያችሁ ከገዢው ፓርቲ ጋር ሊዋሃድ ይችላል ተብሎ ይገመታል ምላሻችሁ ምንድነው ሲል ጠይቋል፡፡

እስካሁን ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ውህደትን በተመለከተ ያደረግነው ውይይት የለም፤ ነገር ግን የፓርቲውን ፕሮግራም አይተን ልንዋሃድ እንችላለን፡፡ ብልጽግናም በሩ ክፍት መሆኑን እንውቃለን ሲሉ የፓርቲው ከፍተኛ ሊቀመንበር ዶክተር አረጋዊ በርሔ ተናግረዋል፡፡

(ምንጭ:-ኢትዮ ኤፍኤም)

Click to comment

More in ዜና

Trending

Advertisement News.et Ad
To Top