Connect with us

ላስቬጋሶች ተነስተዋል

ላስቬጋሶች ተነስተዋል
አብመድ

ዜና

ላስቬጋሶች ተነስተዋል

ላስቬጋሶች ተነስተዋል

በላስ ቬጋስ ነዋሪ  የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ ኤርትራውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ባደረጉት ሰልፍ የህወሃት ቡድን የፈፀመውን የሰላም ማደፍረስ እና የክህደት ወንጀል አውግዘዋል።

በሕወሃት ስርዓት ተጠቃሚ በሆኑ የዳያስፖራ ቡድን አባላት ግፊት በኢትዮጵያ ላይ በአንዳንድ የአሜሪካ የሕግ አውጪ እና የሕግ አስፈፃሚ አካላት የሚደረገውን ያልተገባ ዲፕሎማሲያዊ ጫናን ተቃውመዋል።

የዳያስፖራ አባላቱ ለሀገራቸው እና ለመንግሥት ያላቸውን ድጋፍ ገልጸዋል።

በዲፕሎማሲው ረገድ በኢትዮጵያ ላይ የሚደረገውን ኢ-ፍትሐዊ  ጫና በተደራጀ መንገድ ለመቋቋምና ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት ለመታገል መወሰናቸውን አረጋግጠዋል።

ሰልፈኞቹ የጁንታው ቡድን እና ተባባሪዎቹ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የፈፀሙትን አሰቃቂ ወንጀሎች በማውገዝ፣ አሜሪካን ጨምሮ የዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ ጉዳዩን በጥንቃቄ በመመርመር ትክክለኛ ውሳኔ እንዲሰጥ ጥሪ የሚያቀርቡ እና ሌሎችም መልዕክቶችንም አስተላልፈዋል።

ሰልፈኞቹ ጥያቄያቸውን በኔቫዳ ግዛት ተመራጭ ለሆኑ ሁለት ሴናተሮች እና አራት የኮንግረስ አባላት በጽሑፍ አቅርበዋል።

በሰልፉ ሥነ-ሥርዓት ላይ በርካታ የላስቬጋስ ከተማ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን፣ ኤርትራውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ተሳትፈዋል።

ሰልፉን በላስ ቬጋስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ እና የላስ ቬጋስ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ንዑስ ቡድን አባላት ማስተባበራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።(አብመድ)

 

Click to comment

More in ዜና

Trending

Advertisement News.et Ad
To Top