Connect with us

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መታሰራቸው ቅሬታ አስነሳ

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መታሰራቸው ቅሬታ አስነሳ
Photo: Social Media

ህግና ስርዓት

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መታሰራቸው ቅሬታ አስነሳ

ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ ከቤታቸው የተያዙት ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ያለ ፍርድ እስር ቤት እንደሚገኙ ነው ጠበቃቸው የተናገሩት፡፡

የኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ጠበቃ የሆኑት አቶ አዲሱ ጌታነህ ደንበኛዬ ከተያዘ ሁለት ወር እንደሞላው ተናግረው በነዚህ ሁሉ ጊዜያቶች ውስጥ ፖሊስ ለምርመራ ጊዜ እየወሰደ ፍርድ ቤትም ተገቢ ያለውን ጊዜ እየሰጠ እስካሁን ድረስ ቆይተናል፡፡

ነገር ግን ፖሊስ ምርመራዬን ጨርሻለሁ ብሎ ለፍርድ ቤት ካስረከበ እና መዝገቡም ለአቃቢ ህግ የሰጠው ነሀሴ 13 ነው ስለዚህ የምርመራ መዝገቡ ከተዘጋ ኢንጂነር ይልቃል በዋስ መውጣት ይገባቸው ነበር ያ ግን ሊሆን አልቻለም ብለዋል፡፡

አቃቢ ህግ በእለቱ ቀርቦ ክስ ለመመስረት የ15 ቀን ቀነ ገደብ እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት በደብዳቤ ጠይቆ ፍርድ ቤትም 10 ቀን በቂ ስለሆነ አቃቢ ህግ በዚህ ቀን ክስ እንዲመሰረት ሲል ትዛዝ ሰቶ ነበር፡፡

ነገር ግን ፍርድ ቤት የሰጠው ቀን ነሀሴ 22 ነበር ለሶስት ቀናት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሳይኖር ደንበኛዬ እስር ቤት ተቀምጠዋል ብለዋል ጠበቃ አዲሱ ጌታነህ፡፡

የፍትህ ስርአት ማሻሻያ እየተደረገ ነው እየተባለ ባለበት ወቅት እንደዚህ ያሉ የመብት ጥሰቶች የሚደረጉ ከሆነ የህግ ስርአቱን ይጎጋዋል ሲሉም ተናግዋል አቶ አዲሱ፡፡

ደንበኛዬ አሁንም ቢሆን መጠርጠር የሚያስችል በቂ የሆነ ማስረጃ ያስፈልጋል ያሉት አቶ አዲሱ ከልክ በላይ ምርመራም ማድረግ አያስፈልግም ነበር ብለዋል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም፡፡

(ኢትዮ ኤፍ ኤም )

Click to comment

More in ህግና ስርዓት

Trending

Advertisement News.et Ad
To Top