Connect with us

ውሻ ይዛ መስጅድ የገባችው ሴት ምህረት ተደረገላት

ውሻ ይዛ መስጅድ የገባችው ሴት ምህረት ተደረገላት
Photo: Facebook

ባህልና ታሪክ

ውሻ ይዛ መስጅድ የገባችው ሴት ምህረት ተደረገላት


ሱዜት ማርጋሬት የተባለችው ሴት ጫማዋን ሳታወልቅ እና ውሻዋን አስከትላ ወደ መስጅድ ስትገባ የሚያሳያው ተንቀሳቃሽ ምስል በርካታ ኢንዶኔዢያዊያን ተጋርተውታል።

የማርጋሬት ተግባር በርካታ የዕምነቱን ተከታዮች አበሳጭቷል።

ውሾች በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በስፋት ንጹህ እንዳልሆኑ ይታመናል።

በማርጋሬት ላይ የቀረበውን ክስ መርምረው የፍርድ ውሳኔ ለመስጠት የተሰየሙት ዳኞች፤ ተከሳሿ የአእምሮ ጤና መቃወያስ ያጋጠማት በመሆኗ ሃይማኖትን በመዳፈር በሚል ብይን መስጠት አንችልም ሲሉ በነጻ አሰናብተዋታል።
በርካቶች በተጋሩት ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ፤ ማርጋሬት የካቶሊክ ዕምነት ተከታይ መሆኗን በመጥቀስ ጫማዋን ሳታወልቅ ውሻዋን አስከትላ ወደ መስጅዱ ከገባች በኋላ፤ ባለቤቷ በመስጅዱ የሰርግ ስርዓቱን ለማከናወን ቀጠሮ መያዙን በብስጭት መናገር ትጀምራለች።

ማርጋሬት ባለቤቷ እምቱን ወደ እስልምና ለመቀየሩ መስጅዱን ተጠያቂ ያደረገች ሲሆን፤ መስጅዱን ለቃ እንድትወጣ የሞከረን ጥበቃ ለመማታትም ሞክራለች።

የመስጅዱ መሪዎች ማርጋሬት ስለምትለው ግለሰብም ይሁን ስለተያዘ የሰርግ ቀጠሮ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።

ማርጋሬት የተባለው ችግር ባይኖርባት ድርጊቷ ቢያንስ ስምንት ወራትን በእስር እንድታሳለፍ ያስችላት ነበር ተብሏል።

ምንጭ:-  BBC

Continue Reading
Advertisement News.et Ad
You may also like...
Click to comment

More in ባህልና ታሪክ

Trending

Advertisement News.et Ad
To Top