Connect with us

25 ሺህ ደቡብ ኮርያውያን ሳይሞቱ ቀብራቸው ተፈጽሟል

25 ሺህ ደቡብ ኮርያውያን ሳይሞቱ ቀብራቸው ተፈጽሟል
Photo: Reuters

አስገራሚ

25 ሺህ ደቡብ ኮርያውያን ሳይሞቱ ቀብራቸው ተፈጽሟል

በደቡብ ኮርያ ፈቃደኛ ለሆኑ ሰዎች በህይወት እያሉ የቀብር ስነስርዓት በተሳካ ሁኔታ የመፈጸም አገልግሎት የሚሰጥ በአይነቱ ለየት ያለ ድርጅት መቋቋሙንና ከ25 ሺህ በላይ የአገሪቱ ዜጎች በዚህ ድርጅት አማካይነት ሳይሞቱ ቀብራቸው መፈጸሙን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ሆዮዎን ሂሊንግ ሴንተር የሚል ስያሜ ያለውና ከሰባት አመታት በፊት የተቋቋመው ድርጅቱ፤ ሰዎች በቁም እያሉ የቀብር ስነስርኣታቸውን በመፈጸም፣ ሞትን እንዲያስታውሱና ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ የሚያስችል አገልግሎት የመስጠት ዓላማ እንዳለው የጠቆመው ዘገባው፣ እስካሁን ድረስም ከ25 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች አገልግሎቱን መስጠቱን አመልክቷል፡፡

“እንደምትሞት በቅጡ ከተረዳህና ሞትን በህይወት እያለህ ከተለማመድከው፣ ህይወትህን የምትመራበትን መንገድና አኗኗርህን ትለውጣለህ” ያሉት የ75 አመቱ የዕድሜ ባለጸጋ ቾ ጃሂ፤ “በጥሩ ሁኔታ መሞት” በተሰኘውና በድርጅቱ በሚሰጠው የጅምላ የቀርብ ስነስርዓት ላይ ቀብራቸውን ማስፈጸማቸውን ተናግረዋል፡፡

ድርጅቱ በቅርቡ ባከናወነው የጋራ የቀብር ስነስርኣት ላይ ህጻናትና አረጋውያንን እንዲሁም ቀሳውስትንና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው ደቡብ ኮርያውያን መሳተፋቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ሰዎቹ በሬሳ ሳጥን ውስጥ ተጋድመው ለ10 ደቂቃ ያህል በመቆየት ቀብራቸው መፈጸሙንም አመልክቷል፡፡

ድርጅቱ በህይወት እያሉ የቀርብ ስነስርዓታቸውን እንዲያከብሩ በማድረግ ዜጎች ለህይወታቸው ዋጋ እንዲሰጡ፣ የበደሏቸውን ይቅር እንዲሉና ኑሯቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲመሩ የማገዝ ራዕይ ሰንቆ ስራ መጀመሩንና የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ቁጥርም ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ዘገባው አስታውቋል፡፡

Continue Reading
Advertisement News.et Ad
You may also like...
Click to comment

More in አስገራሚ

Trending

Advertisement News.et Ad
To Top